ወቅታዊው የፖለቲካ ቀውስ እና የኢትዮጵያ አንድነት ጥያቄ
እሑድ፣ ሐምሌ 7 2011ማስታወቂያ
እያደር ብልጭ ያሉት አንዳንድ አጋጣሚዎች እና ከመንግሥት ወገን ጥርት ያለ መረጃ እጥረቱ እንዳለ ሆኖ ከድንገቴው የከፍተኛ ወታደራዊ እና ፖለቲካ ባለሥልጣናት ግድያ በኋላ የጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ፓርቲ አባላት እስራት ዳግም ሌላ የስጋት ምክንያት ሆኗል። በሌላ በኩል በክልሎች መካከል የሚታየው ፉክክር እንዲሁም በገዢው ግንባት አባላት መካከል ጎልቶ የወጣው አለመግባባት ኢትዮጵያን አቅጣጫው ወዳልታወቀ ዕጣ ፈንታ እየገፋት እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ። የክልል እንሁን ጥያቄዎች፣ የድንበር እና ግዛት ጉዳዮች ሀገር እንደ ሀገር የመቀጠሏን ጉዳይ አሳሳቢ እና እንቆቅልሽ አድርጎታል። ወቅታዊው የፖለቲካ ቀውስ እና የኢትዮጵያ አንድነት ጥያቄ የዚህ ሳምንት የዶይቼ ቬለ እንወያይ ርዕስ ነው። ሙሉ ውይይቱን ከድምፅ ዘገባው ይከታተሉ።
ሸዋዬ ለገሠ