ከአቶ አባዱላ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ
ሐሙስ፣ ኅዳር 10 2013ማስታወቂያ
ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት በተለያዩ የሃገሪቱ ከፍተኛ የስልጣን እርከኖች ላይ ሲሰሩ የነበሩት አቶ አባዱላ ገመዳ ከዶይቼ ቬለ ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ በፌዴራሉ እና ትግራይ ክልልን በሚያስተዳድረው "ህወሓት" መካከል የነበሩ የሃሳብ ልዩነቶች ጦር ለመማዘዝም የማያበቁ እንደነበሩ ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ከብልጽግና ፓርቲ ምስረታ በኋላ "የሁለቱ ወገኖች ልዩነት የመጥበብ አዝማሚያን አላሳየም" ያሉት የቀድሞው ጉምቱ ባለስልጣን በተለይም ህወሓት "በፌዴራሉ መንግስትና በህገመንግስቱም ጭምር እውቅና የተነፈገ" ካሉት የትግራዩ ምርጫ በኋላ ግን ነገሮች ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ማምራታቸውን እና የድርድር መስመርን ያጠበቡ ብለውታል፡፡ በህወሓት ባለስልጣንም ጭምር ተረጋግጧል ያሉት የሰሜን ዕዝ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የተወሰደው ያልታሰበ ያሉት ጥቃት ደግሞ "የፌዴራሉ መንግስት ተገዶ ወደ ጦርነት ለመግባቱ ማሳያ ነው" ያሉት አቶ አባዱላ አሁን ሊደርስ የሚችለውን ቀውስ የሚያሳንሰው የጦርነቱን ጊዜ ማሳጠር ብቻ ነው ሲሉም አክለዋል፡፡
ስዩም ጌቱ
ኂሩት መለሰ