ለበዓሉ ወደ አዲስ አበባ የተጓዙ ኢትዮጵያውያን
ማክሰኞ፣ መስከረም 1 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አዲሱን ዓመት በሀገራቸው እንዲያከብሩ ባስተላለፉት ጥሪ መሠረት በርካታ ኢትዮጵያውያን ዐውደ ዓመትን በኢትዮጵያ ለማክበር ሀገራቸው ገብተዋል። ከመካከላቸው ነዋሪነታቸው ብሪታንያ የሆነ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል። የለንደንዋ ዘጋቢያችን ሀና ደምሴ በለንደኑ የሂትሮው አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝታ ለበዓሉ ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ሲጠባበቁ ያገኘቻቸውን ኢትዮጵያውያን እና ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ አድርገው ወደ አስመራ የሚበሩ ኤርትራውያንን አነጋግራለች። ሃና እዚያው ለንደን በተካሄደ የአዲስ ዓመት አቀባበል ስነ ስርዓት ላይም ተገኝታ ነበር። ወደ ዘገባው።
ሃና ደምሴ
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ