1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ለበዓሉ ወደ አዲስ አበባ የተጓዙ ኢትዮጵያውያን 

ማክሰኞ፣ መስከረም 1 2011

የለንደንዋ ዘጋቢያችን ሀና ደምሴ በለንደኑ የሂትሮው አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝታ ለበዓሉ ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ሲጠባበቁ ያገኘቻቸውን ኢትዮጵያውያን እና ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ አድርገው ወደ አስመራ የሚበሩ ኤርትራውያንን አነጋግራለች።

https://p.dw.com/p/34hOI
UK London
ምስል picture-alliance/imageBROKER/V. Wolf

ለበዓሉ ወደ አዲስ አበባ የተጓዙ ኢትዮጵያውያን 

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አዲሱን ዓመት በሀገራቸው እንዲያከብሩ ባስተላለፉት ጥሪ መሠረት በርካታ ኢትዮጵያውያን ዐውደ ዓመትን በኢትዮጵያ ለማክበር ሀገራቸው ገብተዋል። ከመካከላቸው ነዋሪነታቸው ብሪታንያ የሆነ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይገኙበታል። የለንደንዋ ዘጋቢያችን ሀና ደምሴ በለንደኑ የሂትሮው አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝታ ለበዓሉ ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ሲጠባበቁ ያገኘቻቸውን ኢትዮጵያውያን እና ከዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ አድርገው ወደ አስመራ የሚበሩ ኤርትራውያንን አነጋግራለች። ሃና እዚያው ለንደን በተካሄደ የአዲስ ዓመት አቀባበል ስነ ስርዓት ላይም ተገኝታ ነበር። ወደ ዘገባው።


ሃና ደምሴ 
አዜብ ታደሰ 
ኂሩት መለሰ