1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከቤኒሻንጉል ተፈናቅለው ባሕር ዳር የተጠለሉ ዕርዳታ አላገኘንም አሉ

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 10 2011

ተፈናቃዮቹ በከማሺ ዞን ከሚገኘው ቀያቸው እስከ ባሕር ዳር ሲጓዙ በርካታ ፈተና እንደገጠማቸው ተናግረዋል። የአማራ ክልል በበኩሉ አቅሙ የፈቀደውን ያክል እርዳታ እያቀረበ መሆኑን ገልጿል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተዘጋው መንገድ ሲከፈት እና ጸጥታው ሲረጋጋ ወደ ቀያቸው እንደሚመለሱ አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3AOrL
Äthiopien IDPS Benishangul Gumuz
ምስል DW/A. Mekonnen

የክልሉ መንግሥት አቅሙ የፈቀደውን እያቀረበ መሆኑን ገልጿል

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከማሺ ዞን በተቀሰቀሰ ግጭት ተፈናቅለው ባሕር ዳር የተጠለሉ ዜጎች ዕርዳታ አላገኘንም አሉ። ተፈናቃዮቹ በከማሺ ዞን ከሚገኘው ቀያቸው እስከ ባሕር ዳር ሲጓዙ በርካታ ፈተና እንደገጠማቸው ተናግረዋል። የአማራ ክልል በበኩሉ አቅሙ የፈቀደውን ያክል እርዳታ እያቀረበ መሆኑን ገልጿል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተዘጋው መንገድ ሲከፈት እና ጸጥታው ሲረጋጋ ወደ ቀያቸው እንደሚመለሱ አስታውቋል። ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ከመስከረም 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በተከሰተው ግጭት ከ45 ሺሕ በላይ ሰዎች የተፈናቀሉ ሲሆን 670 ዎቹ በባሕር ዳር ከተማ ይገኛሉ። 
ዓለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ