ከታሰሩት መካከል የኢሳት ጋዜጠኛ ይገኝበታል
ረቡዕ፣ ሰኔ 19 2011ማስታወቂያ
ሰኔ 15፣2011 ዓመተ ምህረት ባሕር ዳር እና አዲስ አበባ በተፈጸሙት የከፍተኛ ባለሥልጣናት ግድያዎች ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ የተባሉ ሰዎች አዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር እየዋሉ ነው። ስድስት ተጠርጣሪዎች ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል። ከታሰሩት መካከል የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት አመራር እና አባላት፣ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢሳት ጋዜጠኛ ይገኙበታል። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝሩን አዘጋጅቷል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ