1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኦሮሚያ ክልል ስለተጨፈጨፉ የአማራ ተወላጆች ጉዳይ

ረቡዕ፣ ሰኔ 15 2014

ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች እየተፈጸሙ ያሉትን ግድያዎች ገለልተኛ አካል ጣልቃ ገብቶ በማጥናት ይፋ እንዲያወጣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባት (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንገር (ኦፌኮ) ጠየቁ።

https://p.dw.com/p/4D58u
 Logo Oromo Liberation Front

«ኦነግ እና ኦፌኮ ድርጊቱ በገለልተኛ ወገን ይጣራ»

ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች እየተፈጸሙ ያሉትን ግድያዎች ገለልተኛ አካል ጣል ገብቶ በማጥናት ይፋ እንዲያወጣ የኦሮሞ ነጻነት ግንባት (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንገር (ኦፌኮ) ጠየቁ። ባሳለፍነው የሳምንት መጨረሻ ቅዳሜ ዕለት በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ዞን፣ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ ነዋሪዎች የሆኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ በአብዛኛው የአማራ ብሔር ተወላጆች በታጠቁ ኃይሎች መጨፍጨፋቸው ያስቆጣቸው የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድርጊቱን በማውገዝ ሰሞኑን መግለጫ አውጥተዋል። ዛሬ ጉባኤውን ማካሄድ የጀመረው የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በበኩሉ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የሚፈጸም የትኛውንም ግድያ በመቃወም መግለጫ አውጥቷል።

ሥዩም ጌቱ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ነጋሽ መሐመድ