1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በሳዑዲ ማጎሪያዎች

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 7 2013

በድርጅቱ የፍልሰተኞችና ስደተኞች መብት ክፍል ሃላፊ ቢል ፍሬሊክ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ሳዑዲ በሚገኙ የስደተኞች ማጎሪያ ማዕከላት በኢሰብዓዊ መንገድ ነው የተያዙት።አሁን ያሉበት ሁኔታም አስደንጋጭና አሳዛኝ ነው።

https://p.dw.com/p/3mnSJ
Äthiopien Sudan Jobsuche Mekelle Migration
ምስል DW/M. Hailessilasie

«ሂዩመን ራይትስ ዋች ከሳዑዲ አረብያ ቀና ምላሽ አላገኘም»

ሳዑዲ አረብያ የኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አያያዝ እንድታሻሻል ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች ቢጠይቅም ቀና ምላሽ እንዳላገኘ አስታወቀ። በድርጅቱ የፍልሰተኞችና ስደተኞች መብት ክፍል ሃላፊ ቢል ፍሬሊክ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች ሳዑዲ በሚገኙ የስደተኞች ማጎሪያ ማዕከላት በኢሰብዓዊ መንገድ ነው የተያዙት።አሁን ያሉበት ሁኔታም አስደንጋጭና አሳዛኝ ነው። ድርጅቱ በሃገሪቱ የስደተኞች ማጎሪያ ማዕከላት የሚገኙ ኢትዮጵያንን አነጋግሮ ትናንት ይፋ ባደረገው ዘገባው እንደገለጸው በኢሰብዓዊው አያያዝ ምክንያት ከጥቅምት ወዲህ ቢያንስ የሦስት ሰዎች ሕይወት አልፏል።ከአትላንታ ዩናይትድ ስቴትስ ታሪኩ ኃይሉ ተጨማሪ ዘገባ አሰናድቷል።
ታሪኩ ኃይሉ 
ኂሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ