ኢትዮጵያዊነት የዜጎች ማስከበሪያ ጉባኤ በኢትዮጵያ ኢንስቲትዩት ሊከፍት ነው
ቅዳሜ፣ ነሐሴ 11 2011ማስታወቂያ
ኢትዮጵያዊነት የዜጎች ማስከበሪያ ጉባኤ በዩናይትድ ስቴትስ፣ አውሮፓ እና ሌሎች አካባቢዎች ደጋፊ እና አባላት እንዳሉት በአሜሪካ ቺካጎ ክፍለሀገር የሚኖሩት የድርጅቱ ሊቀመንበር ዶ/ር እርቁ ይመር ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ደግሞ ድርጅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ነው ብለዋል።
ድርጅቱ ከዚህ ቀደም በተለያዩ ጊዜያት በህገ መንግስት፣ በምጣኔ ሀብት፣ በትምህርት እና በሌሎችም ጉዳዮች ጥናታዊ ጽሁፎችን ማቅረቡን ሊቀመንበሩ ያስረዳሉ። ከእነዚህ ጥናታዊ ጽሁፎች ውስጥ ሶስቱ ታትመው በታላላቅ የትምህርት ተቋማት እንደሚገኙም ገልጸዋል። አሁን ድርጅታቸው በኢትዮጵያዊነት የጋራ እሴት ላይ ያተኮረው ላለፉት 30 ዓመታት ኢትዮጵያዊነት በመደብዘዙ ነው ብለዋል።
ሙሉ ጥንቅሩን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።
መክብብ ሸዋ
ተስፋለም ወልደየስ