1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የቅርስ ጥበቃ ተቋም የኮሚቴ አባል ሆና ተመረጠች

ዓርብ፣ ኅዳር 19 2012

ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስ እና ባህል ተቋም ዩኔስኮ የአለም ቅርስ ጥበቃ ኮሚቴ አባል ሀገር ሆና ተመርጣለች።

https://p.dw.com/p/3TyvK
GMF16 Logo Unesco
ምስል UNESCO

ኢትዮጵያ በአባልነት የተመረጠችው ፓሪስ በተካሄደው ስብሰባ ነው

ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስ እና ባህል ተቋም ዩኔስኮ የአለም ቅርስ ጥበቃ ኮሚቴ አባል ሀገር ሆና ተመርጣለች። ኢትዮጵያ በአለም አቀፉ የቅርስ ጥበቃ ተቋም የኮሚቴ አባል ሆና በመመረጧ ለዓለም ቅርሶች ጥበቃ ትኩረት እንዲሰጥ የበኩሏን አስተዋጽዖ እንድታበረክት ዕድል ይፈጥርላታል ተብሏል። ኢትዮጵያ በአባልነት የተመረጠችው ሰሞኑን ፓሪስ ላይ በተካሄደው የዩኔስኮ የቅርስ ጥበቃ ኮንቬሽን አባል አገራት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ነው።

ሃማኖት ጥሩነህ 
ታምራት ዲንሳ 
ተስፋለም ወልደየስ