1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አፍሪቃውያንን ያሳሰበው ደቡብ አፍሪቃ አዲስ ሕግ

ሐሙስ፣ መስከረም 22 2012

ደቡብ አፍሪቃ በአነስተኛ ንግድ ልማት ሚንስትሯ በኩል ልታወጣ ያቀደችው አዲስ  ሕግ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የውጭ ሃገራትን በአንዳንድ አነስተኛ ንግድ ላይ እንዳይሰማሩ የሚያግድ ነው።

https://p.dw.com/p/3QhG7
Südafrika Xenophobie Rassismus Unruhen
ምስል Getty Images/G.Guercia

«ኢትዮጵያውያን በብዛት በችርቻሮ ንግድ ተሰማርተው ይገኛሉ።»

ደቡብ አፍሪቃ በአነስተኛ ንግድ ልማት ሚንስትሯ በኩል ልታወጣ ያቀደችው አዲስ  ሕግ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የውጭ ሃገራትን በአንዳንድ አነስተኛ ንግድ ላይ እንዳይሰማሩ የሚያግድ ነው። ይሕ አዲስ  ሕግ የውጭ ሃገራት በመጤ ጠል ደቡብ አፍሪቃውያን መጠነ-ሰፊ ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ አንዳቸውም ለደረሳባቸው ጉዳት ካሳ ሳያገኙ የሚወጣ መኾኑ ብዙዎችን አስከፍቷል። የውጭ ሃገራት ጥላቻ የወለደው ሕግ ነው፤ ስለዚህ ተቀባይነት የለውም ሲሉ ደቡብ አፍሪቃ ነዋሪ የኾኑ አፍሪቃውያን ይናገራሉ። ደቡብ አፍሪቃ ነዋሪ ከሆነው ጋዜጠኛ እና የመብት ተሟጋች መላኩ አየለ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርገናል። 

ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ