1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አጠያያቂው የአውሮጳ ህብረት አቅምና ተሰሚነት  

ረቡዕ፣ ጥር 6 2012

የአውሮጳ ህብረት በሊቢያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ድጋፍ ያገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር ፋይዝ አልሳራጅን መንግሥት እየደገፈ ነው።ሆኖም ራሳቸውን የብሔራዊ ጦር ጠቅላይ አዛዥ ብለው የሰየሙት የጀነራል ኸሊፋ ሀፍጣር ኃይሎች የሊቢያ መንግሥት መቀመጫ ወደሆነችው ትሪፖሊ ሲገሰግሱ ተጽእኖ ማድረግ አለመቻሉ አቅሙንና ተሰሚነቱን አጠያያቂ አድርጎታል።

https://p.dw.com/p/3WC5p
BG Streik in Europa 2019 l Brexit - Demonstration, Großbritannien London
ምስል Getty Images/AFP/N. Hallen'n

አጠያያቂው የአውሮጳ ህብረት አቅምና ተሰሚነት  

የኢራንና የዩናይትድ ስቴትስ ግጭት እንዲሁም የሊቢያው ጦርነት እና የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት የአውሮጳ ህብረትን እየተፈተኑ ነው።ህብረቱ ኢራንን ከዓለም አቀፉ ማህብረሰብ ጋር ለማስማማት ብዙ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ኢራን ኒዩክልየርን  ለሰላማዊ ጥቅም ብቻ እንድታውል የተስማማችበት የኒዩክልየር ውል ላይ እንድትደርስ ብዙ አስተዋጽኦም አድርጎ ነበር ።በሊቢያም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ድጋፍ ያገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር ፋይዝ አል-ሳራጅን መንግሥት እየደገፈ ነው። ሆኖም ራሳቸውን የብሔራዊ ጦር ጠቅላይ አዛዥ ብለው የሰየሙት የጀነራል ኸሊፋ ሀፍጣር ኃይሎች የሊቢያ መንግሥት መቀመጫ ወደሆነችው ትሪፖሊ ሲገሰግሱ ህብረቱ ተጽእኖ ማድረግ አለመቻሉ እያነጋገረ ነው። የዛሬው አውሮጳ እና ጀርመን ዝግጅታችን በአጠያያቂው የአውሮጳ ህብረት አቅምና ተሰሚነት ላይ ያተኩራል። ገበያው ንጉሤ ያቀርብልናል።
ገበያው ንጉሤ
ኂሩት መለሰ