1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲስ የስደተኞች ውል

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 2 2011

ከትናንት ጀምሮ ማራካሽ ሞሮኮ ላይ የተሰባሰቡት የዓለም መንግሥታት መሪዎች እና ተወካዮች የተመድ በስደተኞች ጉዳይ ያቀረበውን ዓለም አቀፍ የስደተኞች ውል በመቀበል አጽድቀዋል።

https://p.dw.com/p/39t8A
Marrakesch  UN-Migrationskonferenz Logos
ምስል picture-alliance/dpa/E. Lalmand

«ውሉ ሕጋዊ አሳሪነት የለውም»

በጎርጎሪዮሳዊው 2015ዓ.ም በአውሮጳ የተከሰተውን የስደተኞች ቀውስ ተከትሎ የተሰዳጆች ጉዳይ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል። የመንግሥታቱ ድርጅት ታዲያ ችግሩ በጋራ ኃላፊነት እና ትብብር ለመፍታት ያስችላል ብሎ ይህን ውል አዘጋጅቶ መንግሥታቱ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲደራደሩበት ነበር። እንዲያም ሆኖ ስደተኞችን በተመለከተ የመንግሥታቱ ድርጅት ጫና ሊያደርግ ነው ከሚል ስጋት የውሉ ምንነት ሃገራትን ሲያሳስብ እንደቆየ ነው የተነገረው። አሁን መንግሥታት የተስማሙበት ውል አስገዳጅ አለመሆኑም ተመልክቷል። ዘጋብያችን ከብራስልስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ገበያው ንጉሤ

ሸዋዬ ለገሠ

እሸቴ በቀለ