1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የስደተኞች ረቂቅ ሕግ 

ማክሰኞ፣ ኅዳር 23 2012

በአዲሱ እቅድ መንግሥት ከአሠሪዎች ጋር የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ያሉባቸውን የሥራ መስኮች ለይቶ እንደሚያቀርብ ፤ክፈቱቱን ለመሙላትም ለቦታው አስፈላጊ የሆኑ የውጭ ዜጎችን ቅጥር እንደሚያመቻች አስታውቋል።ሆኖም አሠሪዎች በክፍት የሥራ ቦታቸው የፈረንሳይ ዜጋ መቅጠር ያልቻሉበትን ምክንያት ማስረዳት ይኖርባቸዋል።

https://p.dw.com/p/3U9QI
Paris Regierung zu Migranten-Programm
ምስል AFP/D. Faget

የፈረንሳይ የስደተኞች ረቂቅ ሕግ 

ፈረንሳይ የውጭ ዜጎችን ለሥራ በኮታ ወደ ሃገርዋ የማስገባት እቅድ እንዳወጣች መንግሥት በቅርቡ አስታውቋል።ይኽው የኮታ አሠራር በመጪው ዓመት በሃገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥራ ላይ ይውሏል ተብሏል። በአዲሱ እቅድ መንግሥት ከአሠሪዎች ጋር የሰለጠነ የሰው ኃይል እጥረት ያሉባቸውን የሥራ መስኮች ለይቶ እንደሚያቀርብ ፤ክፈቱቱን ለመሙላትም ለቦታው አስፈላጊ የሆኑ የውጭ ዜጎችን ቅጥር እንደሚያመቻች አስታውቋል።ሆኖም አሠሪዎች በክፍት የሥራ ቦታቸው የፈረንሳይ ዜጋ መቅጠር ያልቻሉበትን ምክንያት ማስረዳት ይኖርባቸዋል።

Frankreich | Premierminister Edouard Philippe
ምስል AFP/Getty Images/I. Langsdon

የሠለጠነ የውጭ ባለሞያን ወደ ፈረንሳይ የማስገባቱ እቅድ ከቀኝ ጽንፈኞች እና የውጭ ዜጎች ፈረንሳይ መግባታቸውን ከሚቃወሙ ወገኖች ተቃውሞ እየቀረበበት ነው።ዝርዝሩን የፓሪስዋ ዘጋቢያችን ሃያማኖት ጥሩነህ በዛሬው አውሮጳ እና ጀርመን ዝግጅታችን ታቀርብልናለች።
ሃይማኖት ጥሩነህ 
ኂሩት መለሰ