1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲሱ የእስራኤል መንግሥት

ሰኞ፣ ሰኔ 7 2013

በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ዛሬ ቃለ መሃላ የፈጸሙት የ49 ዓመቱ የአይሁድ ብሔረተኞች ፓርቲ መሪ ናፍታሊ ቤኔት ሰላሳ ስድስተኛውን የእስራኤል መንግሥት ዛሬ መስርተዋል። ። ዛሬ በተሰየመው የአዲሱ መንግሥት ካቢኔ ውስጥ ትውልደ ኢትዮጵያዊት ሚኒስትር ይገኙበታል።

https://p.dw.com/p/3utzy
Israel | Politik Koalitionsbildung
ምስል Ariel Schalit/AP/picture alliance

አዲሱ የእስራኤል መንግሥት

በእስራኤል ዛሬ አዲስ መንግሥት ተመስርቷል። የቤንያሚን ነታንያሁ የ12 ዓመታት የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣን ዛሬ አብቅቷል። የተለያየ አቋም የያዙ ፓርቲዎች የተሰባሰቡበት ሰላሳ ስድስተኛው የእስራኤል መንግሥት ዛሬ ሥራውን ጀምሯል። በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ዛሬ ቃለ መሃላ የፈጸሙት የ49 ዓመቱ የአይሁድ ብሔረተኞች ፓርቲ መሪ ናፍታሊ ቤኔት ከሀገሪቱ ብሔራዊ የፀጥታ ጉዳዮች አማካሪ ማብራሪያ ተስጥቷቸዋል። ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደንም ጋር በስልክ ተወያይተዋል። ዛሬ በተሰየመው የአዲሱ መንግሥት ካቢኔ ውስጥ ትውልደ ኢትዮጵያዊት ሚኒስትር ይገኙበታል። ስለ አዲሱ መንግሥት ምንነት ፈተናዎቹና የህዝቡና የመገናና ብዙሀን አስተያየት የኢየሩሳሌሙን ዘጋቢያችንን አነጋግረናዋል።


ሰሎሞን ሙጬ


ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ