1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲሱ ልውጡ ተዋሲ ያሳደረው ስጋት

ዓርብ፣ ኅዳር 17 2014

በዓለም ዙሪያ አምስት ሚሊዮን ህዝብ የገደለው የኮሮና ተህዋሲ በተከሰተ በሁለት ዓመቱ ከደቡብ አፍሪቃ ተዛመተ የተባለው አዲሱ ልውጥ የኮሮና ተኅዋሲ በዓይነቱ  ዴልታ ከተባለው ልውጥ ተኅዋሲ በበለጠ ፍጥነት የሚዛመት ነው ተብሏል። የአውሮጳ ኅብረት  ከደቡብ አፍሪቃ ና ወደ ደቡብ አፍሪቃ የሚደረጉ በረራዎች መታገድ አለባቸው ሲል አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/43YJZ
USA | Coronavirus Variante SARS-CoV-2
ምስል NIAID-RML/AP/dpa/picture alliance

አዲሱ ልውጡ ተዋሲ ያሳደረው ስጋት

አዲስ ልውጥ የኮሮና ተኅዋሲ ደቡብ አፍሪቃ መገኘቱ ከታወቀ በኋላ ሃገራት  የተለያዩ ማስጠንቀቂያዎችን እየሰጡና እርምጃዎችንም ለመውሰድ እየተዘጋጁ  ነው። በዓለም ዙሪያ አምስት ሚሊዮን ህዝብ የገደለው የኮሮና ተህዋሲ በተከሰተ በሁለት ዓመቱ ከደቡብ አፍሪቃ ተዛመተ የተባለው አዲሱ ልውጥ የኮሮና ተኅዋሲ በዓይነቱ  ዴልታ ከተባለው ልውጥ ተኅዋሲ በበለጠ ፍጥነት የሚዛመት ነው ተብሏል። የአውሮጳ ኅብረት  ከደቡብ አፍሪቃ ና ወደ ደቡብ አፍሪቃ የሚደረጉ በረራዎች መታገድ አለባቸው ሲል አስታውቋል።ቤልጂየም በተኅዋሲው የተያዘ ሰው በሀገርዋ እንደተገኘ ያሳወቀች የመጀመሪያዋ የአውሮፓ ኅብረት አባል ሃገር ሆናለት።ገበያው ንጉሴ ከብራሰልስ ዘገባ አለው ።