የዋጋ ንረት በዘመነ ኮሮና
ረቡዕ፣ ግንቦት 5 2012ማስታወቂያ
የኮሮና ወረርሽኝ ያሳደረው የምጣኔ ሀብት ጫና ስራ አጥነትንና የዋጋ ንረትን በማባባስ የኑሮ ውድነት በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር ማድረጉን ነጋዴዎችም ሸማቾችም ይናገራሉ። ነጋዴዎች ከአከፋፋዮች ሸቀጦችን ከዚህ በፊት ከነበረው ዋጋ ጨምረው እንደሚረከቡ እና የትራንስፖርት ተጨማሪ ወጪ በመኖሩ የምርት መወደድ ማስከተሉን ተናግረዋል።ችግሩ የኑሮ ብቻ ሳይሆን የስነልቦና ጫናም እንደሚያሳርፍ የገለጹ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ መንግስት ከወትሮው በተለየ በገበያ ውስጥ ጣልቃ በመግባት ቁጥጥሩን እንዲያጠብቅ ጠይቀዋል።ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዘገባ አለው።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ