አርበኞች ግንቦት 7 መልዕክት
እሑድ፣ ጳጉሜን 4 2010ማስታወቂያ
ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በቅርቡ ባደረገዉ ሥምምነት መሠረት የትጥቅ ዉጊያዉን ያቆመዉ አርበኞች ግንቦት ሰባት የአንድነት እና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ዉስጥ የተመጀረዉ ለዉጥ እንዳይቀለበስ በንቃት እንደሚታገል የንቅናቄዉ ሊቀመንበር ብርሐኑ ነጋ አስታወቁ። የንቅናቄዉን ከፍተኛ መሪዎች አስከትለዉ ዛሬ አዲስ አበባ የገቡት ዶክተር ብርሐኑ ነጋ አቀባበል ላደረገላቸዉ ሕዝብ እንደነገሩት ፓርቲያቸዉ ኢትዮጵያን ለማረጋጋት እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማስረፅ በፅኑ እንደሚታገልም ገልፀዋል።የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ መሪዎች ዛሬ አዲስ አበባ ሲገቡ የመንግስት ባለሥልጣናት እና የከተማይቱ ሕዝብ ደማቅ አቀባበል አድርገዉላቸዋል።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ነጋሽ መሐመድ