1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አማራ ክልል የማሕፀን ካንሰር መከላከያ ክትባት 

ሐሙስ፣ የካቲት 25 2013

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ካለፈዉ ጥር ጀምሮ ከግማሽ ሚሊዮን ለሚበልጡ ታዳጊ ልጃገረዶች የማሕፀን ጫፍ ነቀርሳ (ካንሰር) መከላከያ ክትባት መስጡትን አስታወቀ።የቢሮዉ ኃላፊዎች እንዳሉት ክትባቱ የተሰጠዉ ከ9ኝ እስከ 14 ዓመት ለሆናቸዉ ልጃገረዶች ነዉ።

https://p.dw.com/p/3qDyh
Symbolbild Pilzinfektion im Genitalbereich
ምስል Colourbox

በአማራ ክልል የማሕጸን ካንሰር ክትባት መሰጠቱ

አማራ ክልል የማሕፀን ካንሰር መከላከያ ክትባት 
የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ካለፈዉ ጥር ጀምሮ ከግማሽ ሚሊዮን ለሚበልጡ ታዳጊ ልጃገረዶች የማሕፀን ጫፍ ነቀርሳ (ካንሰር) መከላከያ ክትባት መስጡትን አስታወቀ።የቢሮዉ ኃላፊዎች እንዳሉት ክትባቱ የተሰጠዉ ከ9ኝ እስከ 14 ዓመት ለሆናቸዉ ልጃገረዶች ነዉ። ከግማሽ ሚሊዮን ከሚበልጡት ልጃገረዶች ገሚሱ ለሁለተኛ ዙር የተከተቡ ሲሆን የተቀሩት ክትባቱን ሲወስዱ የመጀመሪያቸዉ ነዉ።የማሕፀን ጫፍ ነቀርሳ በርካታ ሴቶችን የሚገድል ደዌ ነዉ።የጤና ባለሙያዎች እንደሚመክሩት በሽታዉን ለመከላከል አንዲት ሴት ሁለቴ መከተብ አለባት።ክትባቱ ኢትዮጵያ ዉስጥ መሰጥት ከጀመረ  2 ዓመቱ  ነዉ።የባሕርዳሩ ወኪላችን ዓለምነዉ መኮንን ዝርዝር ዘገባ አለዉ።
አለምነው መኮንን

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ስለሺ