1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ችላ ተባልን ያሉ የታጋች ቤተሰቦች ጥሪ

ዓርብ፣ የካቲት 27 2012

በኦሮሚያ ክልል፣ ቄሌም ወለጋ ዞን በደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ የነበሩ የታገቱት ተማሪዎች ጉዳይ ዝም መባሉ አሳስቦናል ሲሉ ቤተ ዘመዶችና ጉዳዩ ያገባናል ያሉ ዜጎች ገለፁ። ተማሪዎቹ መታገታቸው ከተነገረ 93 ቀን እንደሆነው ያመለከቱት ቤተ ዘመዶች መንግሥት ጉዳዩን እየተከታተልኩ ነው ሲል ይገልፅ ነበር አሁን ግን ዝምታን መርጦአል ብለዋል።

https://p.dw.com/p/3Yz2u
Äthiopien | Proteset | Entführte Studenten
ምስል privat

ቤተሰቦች እስከመቼ ያልቅሱ ስትልም ትጠይቃለች?

በኦሮሚያ ክልል፣ ቄሌም ወለጋ ዞን በደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ የነበሩ የታገቱት ተማሪዎች ጉዳይ ዝም መባሉ አሳስቦናል ሲሉ ቤተ ዘመዶችና ጉዳዩ ያገባናል ያሉ ዜጎች ገለፁ። ተማሪዎቹ መታገታቸው ከተነገረ 93 ቀን እንደሆነው ያመለከቱት ቤተ ዘመዶች መንግሥት ጉዳዩን እየተከታተልኩ ነው ሲል ይገልፅ ነበር አሁን ግን ዝምታን መርጦአል ብለዋል። ጉዳዩ ያገባናል ብለው እየተከታተሉ የሚገኙ ወደ አስር የሚሆኑ ወጣቶች በበኩላቸው መንግሥት ከሰጠው መግለጫ የተለየ የሰማነው ነገር የለም፤ እንደውም  የታገቱትን ተማሪዎች ጉዳይ ማንሳት በፖለቲካ የሚስፈርጅ ሆንዋል ይላሉ። በሀገሪቱ የሚገኙ ብዙኃን መገናኛዎች ብሎም ፖለቲከኞች ጉዳዩን ከማንሳት ተቆጥበዋል ሲሉም ቅሬታቸውን አሰምተዋል። 

Äthiopien | Proteset | Entführte Studenten
ምስል privat

ከታገቱት የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል የሆነችዉ እህቴ ሙሉ ዘውዱ ነገር ምን ደረሰ እባካችሁ ጠይቁ ሲል ወደ ዶይቼ ቬለ የደወለው የታጋች ተማሪ ወንድም  በምዕራብ ጎጃም ቡሬ ወረዳ የሚኖሩት ወላጅ እናቴና እና አያቴ ጠዋት ማት በለቅሶ እየደከሙ ነዉ ይላል። የታገቱትን ተማሪዎች ጉዳይ በቅርበት እየተከታተል ነው ግን አሁን መንግሥት ይፋ ካደረገዉ መግለጫ በላይ የምናውቀው ነገር የለም ያለችን በሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ በመስራትዋ የምትታወቀው መምህርት መዓዛ መሃመድ ጉዳዩን ማንሳት በፖለቲካ የሚያስፈርጅ መሆኑን ተናግራለች። ግን የታጋች ቤተሰቦች እስከመቼ ያልቅሱ ? ስትልም ትጠይቃለች።

አዜብ ታደሰ 

ሸዋዬ ለገሠ