ቱኒዚያ ከመረጋጋት ይልቅ ለሌላ ቀውስ ?
ቅዳሜ፣ ሐምሌ 24 2013ማስታወቂያ
የቱኒዚያው ፕሬዚዳንት ካኢስ ሳኤድ ጠቅላይ ሚንስትሩን ጨምሮ የሀገሪቱን ፓርላማ ማገዳቸው ተረጋግታ በቆየችው ቱኒዚያ ላይ ሌላ የፖለቲካ ትኩሳት ይዞባት መጥቷል። የፕሬዚዳንቱን እርምጃ የሚቃወሙ የሀገሪቱ ዜጎች ብርቱ ተ,ቃውሞ እያሰሙ ሲሆን ከፖሊስ ጋር እስከመጋጨት ደርሰዋል። ከ10 ዓመታት በፊት በዓረቡ ዓለም ዓብዮት እንዲቀሰቀስ ምክንያት የነበረችው ቱኒዚያ በወቅቱ የተሳካ አብዮት ስለማካሄዷ ይነገርላታል። አሁን በፕሬዚዳንቱ የተወሰደው እርምጃ የሀገሪቱን ዜጎች ከማ ስቆጣት ኣልፎ ምዕራባውያን ሃገራትም ፕሬዚዳንቱ ለዴሞክራሲ ተገዢ እንዲሆኑ እና እርምጃቸውን እንዲቀለብሱ ጥሪ እያቀረቡ ነው። በሌላ በኩል ምዕራብ አፍራካዊቷ ሀገር ሴራሊዮን የሞት ቅጣትን ያስቀረች ከህገመንግስቷ በማስወገድ 23ኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ሆናለች። የትኩረት በአፍሪካ የዕለቱ መሰናዶ በሁለቱ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል። ለዝግጅቱ ገበያው ንጉሴ
ታምራት ዲንሳ