1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አነጋጋሪው S.3199 ረቂቅ ሕግ

ረቡዕ፣ መጋቢት 21 2014

የረቂቅ ሕጉ ተቃዋሚዎች በኢትዮጵያ ሰላምና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ለማበረታታት በሚል ርዕስ የተረቀቀው ሕግ የኢትዮጵያን ኤኮኖሚ የሚጎዳና ሀገሪቱ ዓለም አቀፍ ብድርም ሆነ እርዳታ እንዳታገኝ የሚከለክል ነው ሲሉ ለዶቼቬለ ተናግረዋል።መጽደቁን የደገፉ ደግሞ ሕጉ ተጠያቂነትን ያስፍናል ሲሉ ሞግተዋል።

https://p.dw.com/p/49Ego
USA Senat stopgap funding bill | Symbolbild
ምስል Ting Shen/Xinhua/picture alliance

አነጋጋሪው ኤስ ሰላሳ አንድ ዘጠና ዘጠኝ ረቂቅ ሕግ

የዩናይትድስቴትስ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የውጭ ግንኙነ ት ኮሚቴ ኢትዮጵያን አስመልክቶ ያቀረበው S 3199 የተሰኘ ረቂቅ ሕግ ማሳለፉ ምሁራንን በተለያየ ጎራ ከፍሎ እያነጋገረ ነው።

የረቂቅ ሕጉ ተቃዋሚዎች በኢትዮጵያ ሰላምና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ለማበረታታት በሚል ርዕስ የተረቀቀው ሕግ የኢትዮጵያን ኤኮኖሚ የሚጎዳና ሀገሪቱ ዓለም አቀፍ ብድርም ሆነ እርዳታ እንዳታገኝ የሚከለክል ነው ሲሉ ለዶቼቬለ ተናግረዋል።መጽደቁን የደገፉ ደግሞ ሕጉ ተጠያቂነትን ያስፍናል ሲሉ ሞግተዋል።ረቂቁ ሕግ የሚሆነዉ የዩናይትድ ስቴትስ ሴኔት፣የሕግ መምሪያ ምክር ቤትና ፕሬዝደንቱ ሲያፀድቁት ነዉ።

ታሪኩ ኃይሉ

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ