የምርጫ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ረቂቅ ሕግ እና ተቃዋሚ ፓርቲዎች
ሐሙስ፣ ሐምሌ 25 2011ማስታወቂያ
ፓርቲዎቹ ዛሬ በኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ ቢሮ በሰጡት የጋራ መግለጫ ሕጉ ላይ ውይይት አድርገንበት የነበር ቢሆንም አሁን የቀረበው ግን ከተወያየንበት ውጭ የሆነና የማናውቀው ሕግ በመሆኑ በምርጫ ቦርድ ክህደት ተፈጽሞብናል ብለዋል። ፓርቲዎቹ እንዳሉት የተዘጋጀው ሕግ ነባር የፓለቲካ ፓርቲዎችን የሚያከስም ፤ አዳዲሶችም እንዳይታሰቡ የሚያደርግ አፋኝ ሕግ ነው። የመንግሥት ሠራተኞች ለምርጫ የሚወዳደሩ ከሆነ የ6 ወር ደሞዛቸው ሳይከፈላቸው መደረግ ይኖርበታል የተባለውም ተገቢ ያልሆነ ነው ካሉ በኋላ ተግባራዊ ይሁን ከተባለ ግን መጀመር ያለበት ከጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ከህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ መሆኑን መንግሥት ሊያረጋግጥ ይገባዋል ሲሉ አሳስበዋል። መንግሥት አጠቃላይ የምርጫ ሥርአቱን አሻሽላለሁ በሚል ቃል የገባውን ነገርም ከመተግበር መቆጠበን እየተገነዘብን በመሆኑ ይህ ሊስተካከል ይገባል ብለዋል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን ልኮልናል።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሠ
እሸቴ በቀለ