1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ብዙ የሚቀረው የጡት ካንሰር ግንዛቤ

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 16 2014

በጎርጎሪዮሳዊው 2020 ዓ,ም በመላው ዓለም 2,3 ሚሊየን ሴቶች ላይ የጡት ካንሰር መገኘቱን የዓለም የጤና ድርጅት ያመለክታል። በዚሁ ዓመትም 685 ሺህዎች በዚሁ ምክንያት ሕይወታቸው አልፏል። በየዓመቱ የጥቅምት ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ የጡት ካንሰር ይታሰባል። አስቀድሞ ችግሩ ከተደረሰበት ለመዳን እንደሚችል ሰዎች እንዲረዱ በየጊዜው ይመከራል።

https://p.dw.com/p/42Cbp
Symbolbild Brustkrebs Untersuchung
ምስል Christin Klose/Themendienst/dpa/picture alliance

«ጥቅምት፤ ስለጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ወር»

ካንሰርም ሆነ ሌሎች ተላላፊ ያልሆኑ ነገር ግን እጅግ አደገኛ የጤና እክሎች የበለጸጉት እና ኑሯቸው የተደላደለ፤ በቂ የሕክምና አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ ሃገራት ችግር ብቻ መሆኑ ከቀረ ሰነባበተ። የዓለም የጤና ድርጅት መረጃ እንደሚያመለክተውም የተሻለ የህክምና ክትትል እና አገልግሎት በሚደረግባቸው ሃገራት በጡት ካንሰር ምክንያት የሚከሰተው ሞት ከጎርጎሪዮሳዊው 1980 እስከ 2020 ድረስ ባለው ጊዜ 40 በመቶ መቀነስ ተችሏል። ይኽ የተሳካው ደግሞ አስቀድሞ በሚደረግ የምርመራ ክትትል እና ህክምና መሆኑን አጽንኦት ሰጥቷል። ኢትዮጵያ ውስጥ ከካንሰር ሕመም ጋር በተገናኘ ብዙዎችን እየጎዳ የሚገኘው ግንባር ቀደሙ የጡት ካንሰር መሆኑን የዘርፉ የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ። ላለፉት 15 ዓመታት በየዓመቱ በጥቅምት ወር ስለጡት ካንሰር ኅብረተሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው ጥረት መደረጉን የሚናገሩት የማትያስ ወንዱ የኢትዮጵያ የካንሰር ማኅበረሰብ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንዱ በቀለ የችግሩን ምንነት በተመለከተ ኅብረተሰቡ በወጉ ተረድቷል ማለት አስቸጋሪ መሆኑን ነው ያመለከቱት። ፒንክ ሎተስ ኢትዮጵያ  የተሰኘ ስለጡት ካንሰር ግንዛቤን ለማስጨበጥ የሚንቀሳቀስ መረዳጃን ከተባባሪዎቻቸው ጋር በመሆን ያቋቋሙት ወይዘሮ ሜሮን ከበደም ትዝብት ተመሳሳይ ነው። ሙሉ ቅንብሩን ከድምጽ ማዕቀፉ ያድምጡ።

Symbolbild Brustkrebs Untersuchung
ምስል Bo Valentino/Zoonar/picture alliance

ሸዋዬ ለገሠ

እሸቴ በቀለ