1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በጦርነት የተጎዱ የአማራ ክልል አካባቢዎች ቅኝት

ሐሙስ፣ የካቲት 3 2014

ለወራት የጦርነት ቀጣና ሆኖ በከረመው የአማራ ክልል ሰሜን ወሎ አንዳንድ አካባቢዎችም ዛሬም የጦርነት ስጋት መኖሩን አካባቢውን ጎብኝቶ የተመለሰው የብራስልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሤ ከኅብረተሰቡ ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ አጋርቶናል።

https://p.dw.com/p/46pWL
Äthiopien | Verwüstungen in Lalibela
ምስል AFP via Getty Images

የዶቼ ቬለ ዘጋቢ እንደተመለከተው

ከ15 ወራት በላይ የዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት አሁንም በተለይ በአፋር ክልል አካባቢ መቀጠሉ ይሰማል። ለወራት የጦርነት ቀጣና ሆኖ በከረመው የአማራ ክልል ሰሜን ወሎ አንዳንድ አካባቢዎችም ዛሬም የጦርነት ስጋት መኖሩን አካባቢውን ጎብኝቶ የተመለሰው የብራስልሱ ዘጋቢያችን ገበያው ንጉሤ ከኅብረተሰቡ ያገኘውን መረጃ ጠቅሶ አጋርቶናል። ከዓለማችን አስደናቂ ቅርሶች አንዱ በሆነው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ የከፋ ጉዳት አለመድረሱን፤ ቅርሶችም አለመመዝበራቸውን ከስፍራው እንደተረዳ፤ ደሴን ጨምሮ ተዘዋውሮ በተመለከታቸው የወሎ ከተሞች ትምህርት ቤቶች ክፉኛ መጎዳታቸውንም ገልጾልናል። ጦርነቱን ለማስቆም ፖለቲካዊ መፍትሄ ሊገኝ እንደሚችል ሆኖም በኅብረተሰቡ ላይ ጦርነቱ ያስከተለው የመንፈስ ስብራት ጠግኖ የኖረውን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ማስቀጠሉ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥቷል። ገበያውን ስቱዲዮ ከመግባቴ አስቀድሜ ያየውን እንዲያጋራን ጠይቄዋለሁ።

ገበያው ንጉሤ 

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ