በጦርነት ለተፈናቀሉ ዕርዳታ ማሰባሰቢያ በፈረንሳይ ተካሔደ
እሑድ፣ ጥቅምት 28 2014ማስታወቂያ
በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ሳቢያ ለተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ዕርዳታ የሚያሰባስብ መርሐ-ግብር በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ትናንት ቅዳሜ ተካሔደ። በዕርዳታ ማሰባሰቢያው መርሐ ግብር በተለያዩ የፈረንሳይ ከተሞች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል። በመርሐ-ግብሩ የታደሙ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጋቸውን በፓሪስ የዶይቼ ቬለ ወኪል ሐይማኖት ጥሩነሕ ዘግባለች። የገቢ ማሰባሰቢያውን ያዘጋጁት በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ ማኅበር እና ዲፌንድ ኢትዮጵያ ታስክ ፎርስ የተባሉ ቡድኖች ናቸው።
ሐይማኖት ጥሩነሕ
እሸቴ በቀለ