1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በጅንካ ከተማና አካባቢው ጥቃት የደረሰባችው ነዋሪዎች ስጋት

ሰኞ፣ ሚያዝያ 3 2014

በደቡብ ኦሞ ዞን በጅንካ ከተማና አካባቢው በተቀሰቀሰ ሁከት ጥቃት የደረሰባችው ነዋሪዎች አሁንም በስጋት ውስጥ  እንደሚገኙ ገለጹ፡፡ የጂንካ ከተማ አጎራባች በሆኑ ወረዳዎች በሺህዎች የሚገመቱ ነዋሪዎች ነፍሳቸውን ለማትረፍ በጸጥታ ተቋማት እና በቤተ ክርሰቲያናት ቅጥር ግቢ ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ ዛሬ ለዶቼ ቬለ DW ተናግረዋል ፡፡

https://p.dw.com/p/49muN
Äthiopien | Jinka town
ምስል South Omo Zone Government

በጂንካ ከተማ በደረሰው ጥፋት ነዋሪዎች አሁንም ስጋት ውስጥ ናቸው

በደቡብ ኦሞ ዞን በጅንካ ከተማና አካባቢው በተቀሰቀሰ ሁከት ጥቃት የደረሰባችው ነዋሪዎች አሁንም በስጋት ውስጥ  እንደሚገኙ ገለጹ፡፡ የጂንካ ከተማ አጎራባች በሆኑ ወረዳዎች በሺህዎች የሚገመቱ ነዋሪዎች ነፍሳቸውን ለማትረፍ በጸጥታ ተቋማት እና በቤተ ክርሰቲያናት ቅጥር ግቢ ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ ዛሬ ለዶቼ ቬለ DW ተናግረዋል ፡፡

ነዋሪዎቹ አንዳሉት የአሪ ብሄር በዞን መዋቅር እንዲደራጅ የሚጠይቁ ወጣቶች ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በቀሰቀሱት ሁከት በሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል ፤ በርካታ መኖሪያ ቤቶችና የንግድ ድርጅቶች በአሳት ወድመዋል፡፡

ሁከቱ የተቀሰቀሰው የአሪ ብሄር አክቲቪስት ነን በሚሉ ግለሰቦች ነው የሚሉት የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳ አሁን ላይ አካባቢውን የማረጋጋት ሥራዎች እየተከናውኑ እንደሚገኙ አስታውቀዋል፡፡

ሸዋንግዛው ወጋየሁ 

ታምራት ዲንሳ

ማንተጋፍቶት ስለሺ