1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በደቡብ ከ62 ሺህ በላይ ሰዎች በወንዝ ሙላት ተፈናቀሉ 

ማክሰኞ፣ መስከረም 11 2014

በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የኦሞ ወንዝ ሞልቶ ከ62 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን አፈናቀለ። የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ቀሰ በቀስ እየሞላ የመጣው የኦሞ ወንዝ የመኖሪያ ቤቶቻቸውን በመዋጡ በአሁኑ ወቅት በኦሞራቴ ከተማ ተጠልለው ይገኛሉ።

https://p.dw.com/p/40c7K
[No title]
ምስል Shewangizaw Wegayehu

ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማትን ጨምሮ 22 የመሰረተ ልማቶች ወድመዋል

በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ የኦሞ ወንዝ ሞልቶ ከ62 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን አፈናቀለ። የአካባቢው ነዋሪዎች ለዶቼ ቬለ (DW) እንዳሉት ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ቀሰ በቀስ እየሞላ የመጣው የኦሞ ወንዝ የመኖሪያ ቤቶቻቸውን በመዋጡ በአሁኑ ወቅት በኦሞራቴ ከተማ ተጠልለው እንደሚገኙ ገልጸዋል። ዶቼ ቬለ (DW) ያነጋገራቸው የዳሰነች ወረዳ ባለስልጣናት በበኩላቸው በወንዝ ሙላቱ ከተፋናቀሉት ሰዎች በተጨማሪ ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማትን ጨምሮ 22 የመሰረተ ልማት ተቋማትን ማወደሙን ተናግረዋል።

ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ  

አዜብ ታደሰ 

ማንተጋፍቶት ስለሺ