በደቡብ ኢትዮጵያ የቀጠለው ሰልፍ
ሰኞ፣ ጥቅምት 29 2014ማስታወቂያ
መንግሥት አሸባሪ ሲል የፈረጃቸውን ህውሓት እና ኦነግ ሸኔን የሚያወግዝ የተቃውሞ ሰልፍ ኢትዮጵያው ውስጥ ቀጥሏል። በዛሬው ዕለትም በሀዋሳ ከተማ ተካሂዷል። ለሰልፈኞቹ ንግግር ያሰሙት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ «የተወረረው የአማራ እና የአፋር ህዝብ ብቻ ሳይሆን መላው ኢትዮጵያውያን ናቸው» በማለት ተናግረዋል። በ1983 ዓም የደረሰበትን ግፍ በመርሳት በኦሮሞ ህዝብ እየነገደ የሚገኘው አነግ ሸኔ አሁን ህውሓትን ወደ ቤተ መንግሥት ለማስገባት እየሠራ ይገኛል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ ይሁን እንጂ ኦነግ ሸኔ ሸኚ እንጂ ገዢ ሊሆን አይችልም ብለዋል።
ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
ሸዋዬ ለገሠ
አዜብ ታደሰ