1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በወንጀል ተጠርጣሪ ባለሥልጣናት

ማክሰኞ፣ ኅዳር 4 2011

በጅጅጋ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር አቶ ሙሳ አደም እንዳሉት በወንጀል የተጠረጠሩ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መያዝ ህዝብ በመንግሥት ላይ እምነት እንዲኖረው የሚያደርግ እንደ ድልም የሚቆጠር እርምጃ ነው። ወንጀለኞችን በመያዝ ሂደት ግን ንጹሀን እንዳይጎዱ የተጠና እርምጃ መወሰድ አለበት ብለዋል።

https://p.dw.com/p/38BjD
Äthiopien verhaftet 63 wegen Verdachts auf Menschenrechtsverletzungen, Korruption. Der Generalstaatsanwalt Berhanu Tsegaye sagte heute (03.11.2018) lokalen Journalisten, dass die Inhaftierung nach fünf Monaten Ermittlungen erfolgt.
ምስል DW/Y. Geberegziabeher

በወንጀል ተጠርጣሪ ባለሥልጣናት የመያዛቸው አንድምታ

ወንጀለኞችን በማሳደድ ሂደት መንግሥት ጥንቃቄ  እንዲያደርግ  አንድ ምሁር አሳሰቡ። ዶቼቬለ ያነጋገራቸው በጅጅጋ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር አቶ ሙሳ አደም እንዳሉት በወንጀል የተጠረጠሩ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መያዝ ህዝብ በመንግሥት ላይ እምነት እንዲኖረው የሚያደርግ እንደ ድልም የሚቆጠር እርምጃ ነው። ወንጀለኞችን በመያዝ ሂደት ግን ንጹሀን እንዳይጎዱ የተጠና እርምጃ መወሰድ አለበት ብለዋል። በርሳቸው አስተያየት ቁጥጥር ካልተደረገ «የደነገጠ» ያሉት ቡድን ወደ አሉታዊ መንገድ ሊሄድ ይችላል። አቶ ሙሳን ሂሩት መለሰ አነጋግራቸዋለች። አቶ ሙሳ ከአሁኑ የመንግሥት እርምጃ በኋላ ሊጠበቅ የሚችለውን እና መንግሥትም ሆነ ህዝቡ ተጠርጣሪዎችን ተጠያቂ በማድረግ ሂደት ሊከተሉ ይገባል የሚሉትን አቅጣጫ በማስረዳት ይጀምራሉ።   

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ