በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጠ/ሚኒስትሩ ማብራሪያ
ማክሰኞ፣ የካቲት 15 2014ማስታወቂያ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ጦርነቱን የተሸከመበት አቅም የሚደነቅ ነው አሉ። ኢትዮጵያ በጦርነት ውስጥ ሆናም ቢሆን በግብርና እና ከውጪ የሚገቡ ሸቀጦችን በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት ያደረገችው ጥረት እና የተሰበሰበው ገቢ ከፍተኛ መሆንን በስኬትነት አንስተዋል። ቂም እና ሌብነት የኢትዮጵያ የዘመናት የቁልቁለት ጉዞ ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውን የተናገሩት ዐቢይ ዘላቂ ሰላም ለመገንባት ሲባል የሕወሓት ከፍተኛ አመራር የነበሩ ሰዎች ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉን ተናግረዋል። አክለውም እስካሁን ከሕወሓት ጋር የተደረገ ድርድር የለም፤ ይህ ማለት ግን ድርድር አይኖርም ማለት አይደለምም ነው ያሉት።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ