1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የው/ጉ/ሚ ቃል አቀባይ መግለጫ

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 6 2014

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሳምንታዊው ጋዜጣዊ መግለጫቸው ከተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ጋር ለተያያዙ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

https://p.dw.com/p/49xOK
Äthiopien | Botschafter Dina Mufti
ምስል Solomon Muchie/DW

የው/ጉ/ሚ/ ቃል አቀባይ መግለጫ

በትግራይ ክልል እና በፌዴራል መንግሥት መካከል ሰላም እንዲወርድ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙትን የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆን የሥራ ሂደትን በተመለከተ በተጨባጭ እዚህ ላይ ደርሰዋል ለማለት እንደማይቻል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። ልዩ ልዑኩ ግን የሰላም ጥረታቸውን ቀጥለዋል ተብሏል። ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት በጉዳይ ፈፃሚ ደረጃ ለማስቀጠል መወሰኗ የሁለቱ ሃገራት ግንኙነት ችግር እንዳለው አያመለክትም ሲሉ የሚኒስቴሩ ቃል ዐቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናግረዋል። መንግሥት በሳውዲ አረቢያ በስቃይና በችግር ውስጥ ከሚገኙ ዜጎች መካከል ከሰባት ሺህ የሚበልጡትን ኢትዮጵያዊያን በሳምንት ለሦስት ቀናት ፣ በቀን ሦስት ጊዜ በሚደረግ በረራ መመለሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። ይኽ ሥራውም ይቀጥላል ተብሏል።

ሰሎሞን ሙጬ 

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ