ትምህርት
በኦሮሚያ የትምህርት ዳግም መጀመር
ረቡዕ፣ ኅዳር 23 2013ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ክልል በሁሉም አከባቢዎች ባሉት ትምህርት ቤቶች ካለፈዉ ሰኞ ኅዳር 21 ቀን፣ 2013 ዓ.ም ጀምሮ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል መደበኛ ትምሕርት መጀመራቸዉ ተገለጠ። እስካሁንም በክልሉ ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ከሚጠበቁ 11.2 ሚሊየን ተማሪዎች መካከል 9.3 ሚሊዮን ያህሉ መመዝገባቸው ተጠቁሟል። ቀሪዎቹ ተማሪዎች በዚሁ ሁለት ሳምንታት ውስጥ ወደ የትምህርት ቤቶቹ ይመለሳሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ሥዩም ጌቱ ተጨማሪ ጥንቅር ልኳል።
ሥዩም ጌቱ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ