1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በእነ እስክንድር ነጋ ላይ ምስክር በግልጽ ችሎት እንዲቀርብ ተወሰነ

ማክሰኞ፣ ሰኔ 22 2013

የፌዴራል ከፍተኛ  ፍርድ ቤት 1ኛ የጸረ ሽብር እና ሕገ  መንግስታዊ ወንጀሎች ችሎት  በእነእስክንድር ነጋ መዝገብ የተከሰሱ አራት የባልደራስ አባላት ምስክር የመስማት ሂደት በግልጽ ችሎት እንዲታይ ወሰነ።

https://p.dw.com/p/3vkiI
Eskinder Nega - Äthiopien Journalist & Menschenrechtsaktivist
ምስል B. Manaye

በእነ እስክንድር ነጋ ላይ የሚቀርበው ምስክርነት በግልጽ ችሎት እንዲታይ ተወሰነ

የፌዴራል ከፍተኛ  ፍርድ ቤት 1ኛ የጸረ ሽብር እና ሕገ  መንግስታዊ ወንጀሎች ችሎት  በእነእስክንድር ነጋ መዝገብ የተከሰሱ አራት የባልደራስ አባላት ምስክር የመስማት ሂደት በግልጽ ችሎት እንዲታይ ወሰነ። ከተከሳሽ ጠበቆች አንዱ ለዶይቼ ቬለ እንደገለጹት   ፍርድ ቤቱ በሰጠው ተለዋጭ ቀጠሮ ዐቃቤ ሕግ ተጨማሪ ምክንያት ሳያቀርብ እና ተከሳሾች ሳይጉላሉ ብይን እንደሚሰጥ ተስፋቸውን ገልጸዋል። ችሎቱ በዛሬው ውሎው በቀጣይ የዐቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት  ከሐምሌ 8 እስከ 16 ባሉ ቀናት ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።
ዮሐንስ ገብረግዚአብሔር
ታምራት ዲንሳ
ነጋሽ መሐመድ