በእርግዝና እና ከወሊድ በኋላ የሚከሰቱ ችግሮች
ማክሰኞ፣ ጥር 14 2011ማስታወቂያ
በእርግዝና ወቅት እንዲሁም ከወሊድ በኋላ የሚከሰት ደም መፍሰስ ዛሬም ለእናቶች ሞት ዋንኛዉ ምክንያት ነዉ። የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፈው ዓመት ይፋ ያደረገው የእናቶች እና ጨቅላ ሕፃናት ሞት ቅኝት እና ምላሽ መስጠት መርኃ-ግብር እንደሚለው ከ100 እናቶች መካከል 50 ያክሉ በዚሁ በደም መፍሰስ ሳቢያ ሕይወታቸው ያልፋል። ባለፈው ሳምንት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት መቀመጫ በሆነችው የባሕር ዳር ከተማ በዚሁ ጉዳይ ላይ የሚመክር የውይይት መድረክ ተዘጋጅቶ ነበር።
ዓለምነው መኮንን
እሸቴ በቀለ