በኢትዮጵያ ቱሪዝም ላይ ጦርነት እና የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ያጠላው ጥላ
ማክሰኞ፣ መስከረም 18 2014ማስታወቂያ
ባለፈው አንድ ዓመት ኢትዮጵያ ላይ ባጠላው የኮቪድ-19 ዓለማቀፍ ወረርሽኝ እና ጦርነት ሳቢያ አገሪቱ ቢያንስ ከአንድ ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ማጣቷ ተገለጸ፡፡
የቱሪዝም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስከያጅ አቶ ስለሺ ግርማ በተለይ ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት የመሰረታዊ አገልግሎቶች አለመሟላት የሚፈትነው የኢትዮጵያ ቱሪዝም በተለይ በአሁን ወቅት ከፍተኛ ትኩረት ይሰብ የነበረው በሰሜን የአገሪቱ ክፍል ባለው የሰላም እጦት ተደናቅፏል ፡፡
ይህ ደግሞ ኑሮአቸውን በቱሪዝም ይመሩ የነበሩትን ዜጎች ህይወት አደጋ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓል፡፡
ኢንደስትሪውን በኢትዮጵያ ለማዘመን እና ለማሳደግ የተሰሩ ስራዎችም በነዚህ ፈተና ጥያቄ ውስጥ ወድቋል ባይ ናቸው ኃላፊው፡፡
ስዩም ጌቱ
ታምራት ዲንሳ
አዜብ ታደሰ