በአዲስ አበባ በልመና ላይ የተሰማሩት ሶሪያውያን ስደተኞች ሁኔታ
ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 30 2011ማስታወቂያ
የኢሚግሬሽን፣ የዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ ባለፉት አምስት ወራት 560 ሶሪያውያን በህጋዊ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 390ዎቹ ወደ ሃገራቸው መመለሳቸውንም ገልጿል። በኢትዮጵያ ከቀሩት ውስጥ እስካሁን በስደተኝነት በይፋ የተመዘገቡት ግን 96 ብቻ መሆናቸውን የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አስተዳደር ገልጿል።
በህጋዊነት የተመዘገቡትም ይሁን እስካሁን ያልተመዘገቡት ሶርያዊያን ከፍተኛ የሚባል ገንዘብ ወጪ እያደረጉ እንደሚመገቡ እና በህዝብ ሳይሆን በኮንትራት ታክሲዎች እንደሚንቀሳቀሱ የDW ዘጋቢ ታዝቧል። እስከ ሶስት እየሆኑ ለሚከራዩአቸው ቤቶች እስከ 15 ሺህ ብር እንደሚከፍሉም መረጃ አግኝቷል። ሶሪያውያኑ በልመና ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚያገኙ እና ኢትዮጵያዊያን ባለሃብቶችም ከሃገሬው የኔ ቢጤ ድጋፍ ፈላጊዎች ይልቅ ለሶርያዊያኑ ከፍተኛ ገንዘብ በቼክ ሳይቀር እንደሚሰጡ ታዛቢዎች ለDW ተናግረዋል።
ሰለሞን ሙጬ
ተስፋለም ወልደየስ
አርያም ተክሌ