1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በአውሮጳ የኮሮና ክትባት መጓተት

ሐሙስ፣ የካቲት 4 2013

በአውሮጳ የኮሮና ክትባት ሂደት መጓተትና በሩሲያ አንጻር በሚወሰዱ አቋሞች ላይ የፓርላማ አባላትና አንዳንድ አባል መንግሥታት ጭምር በኮሚሽኑ ባለሥልጣናት ላይ ተቃውሞ እያቀረቡ ነው።

https://p.dw.com/p/3pERN
Brüssel I EU I Ursula von der Leyen
ምስል Francois Walschaerts/REUTERS

«ኮሮና ክትባትና የሩሲያ ጉዳይ ማወዛገቡን ቀጥሏል»

በአውሮጳ የኮሮና ክትባት ሂደት መጓተትና በሩሲያ አንጻር በሚወሰዱ አቋሞች ላይ የፓርላማ አባላትና አንዳንድ አባል መንግሥታት ጭምር በኮሚሽኑ ባለሥልጣናት ላይ ተቃውሞ እያቀረቡ ነው። የአውሮጳ ሕብረት ኮሚሽን የውጭ ግንኙነት ኃላፊ ከትናንት በስተያ በአውሮጳ ፓርላማ ቀርበው ባለፈው ዓርብ በሩሲያ ካደረጉት ጉብኝት ጋር ተያይዞና በሩሲያ ላይም ሕብረቱ ባለው ፖሊሲ በሚቀርብባቸው ወቀሳዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የኮሚሽኑ ፕሬዝደንት ዑርዙላ ፎንደር ላይንም በፓርላማው ቀርበው የኮሚሽኑን የኮሮና ክትባት ስልት በማብራራት ከሚቀርብባቸው ክሶችና ወቀሳዎች ራሳቸውንና ኮሚሽናቸውን ተከላክለዋል።

ገበያው ንጉሤ 

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ