1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አስተያየት በአውሮጳ ኅብረት ውሳኔዎች ላይ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 27 2013

ሕብረቱ በምርጫ ታዛቢነት ቢሳተፍ ለምርጫው ተዓማኒነት ትልቅ እድል እንደነበር የገለፁት አስተያየት ሰጪዎቹ ይህ አለመሆኑ ሕብረቱ ይበልጥ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጫናዎችን ለማሳደር እድል እንደሚፈጥርለት ገልጸዋል። በዚህ የተነሳም ኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅሟን ለማስጠበቅ አሁንም ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ሥራዎችን ልታከናውን ይገባል ብለዋል።  

https://p.dw.com/p/3szwS
Äthiopien Besuch des EU-Außenbeauftragten Josep Borrell
ምስል picture-alliance/dpa/European Commission/Eduardo Soteras

የአውሮጳ ኅብረት ምርጫውን ላለመታዘብ ባሳለፈው ውሳኔ ላይ የተሰጡ አስተያየቶች

የአውሮጳ ሕብረት ስድስተኛውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ እንደማይታዘብ ማሳወቁ ሕብረቱ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ላይ ያሳያቸውን አሉታዊ ተፅዕኖዎች እንደሚያመለክት በውሳኔው ላይ አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ ተናገሩ።ሕብረቱ በምርጫ ታዛቢነት ቢሳተፍ ለምርጫው ተዓማኒነት ትልቅ እድል እንደነበር የገለፁት አስተያየት ሰጪዎቹ ይህ አለመሆኑ ሕብረቱ ይበልጥ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ጫናዎችን ለማሳደር እድል እንደሚፈጥርለት ገልጸዋል። በዚህ የተነሳም ኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅሟን ለማስጠበቅ አሁንም ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ሥራዎችን ልታከናውን ይገባል ብለዋል።  
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ