1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በኒሻንጉል ክልል ታጣቂዎች ሰዉ ገደሉ

ማክሰኞ፣ ኅዳር 29 2013

ጥቃቱ የደረሰበት የድባጤ ወረዳ ቂዶ ቀበሌ ነዋሪዎች እንዳሉት ታጣቂዎቹ ባለፈዉ ዕሁድ ከ4 ሰዓት ጀምሮ በከፈቱት ተኩስ የተገደሉት ሰዎች አብዛኞቹ በዕለታዊ ሥራቸዉ ላይ የነበሩ ነበሩ

https://p.dw.com/p/3mRBQ
Karte Äthiopien Metekel EN

«ሟቾቹ በመደበኛ ሥራቸዉ ላይ ነበሩ» እማኝ

በበኒሻጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ማንነታቸዉ በዉል ያልታወቀ ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት በትንሹ 10 ሠላማዊ ሰዎች ገደሉ።ጥቃቱ የደረሰበት የድባጤ ወረዳ ቂዶ ቀበሌ ነዋሪዎች እንዳሉት ታጣቂዎቹ ባለፈዉ ዕሁድ ከ4 ሰዓት ጀምሮ በከፈቱት ተኩስ የተገደሉት ሰዎች አብዛኞቹ በዕለታዊ ሥራቸዉ ላይ የነበሩ ነበሩ።በጥቃቱ ተደናግጠዉ የጠፉ ወይም በታጣቂዎቹ የታግቱ ሰዎች ያሉበት አለመታወቁንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።የመተከል ዞን የአስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር ወይም ኮማንድ ፖስት በዳንጉር ወረዳ የሚንቀሳቀሱ «ፀረ-ሠላም» ኃይላት ባላቸዉ ባላቸዉን 23 ሰዎች ላይ ዕርምጃ መዉሰዱን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ አስታዉቋል።የዕርምጃዉ ምንነት አልተብራራም።

ነጋሳ ደሳለኝ 

ነጋሽ መሐመድ

አዜብ ታደሰ