1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በነበቀለ ገርባ መዝገብና በሌሎች የፍርድ ቤት ዉሎ

ሰኞ፣ ሐምሌ 6 2012

የፌደራል የመጀመርያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በነበቀለ ገርባ መዝገብና በሌሎች በአቃቤ ሕግና በፖሊስ በተያዙ  ተጠርጣሪዎች  ላይ ፖሊስ የጠየቀዉን የምርመራ ጊዜ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ።

https://p.dw.com/p/3fGRW
Äthiopien Politiker Bekele Gerba
ምስል Addis Standard Magazine

ተለዋጭ ቀጠሮ ለሐምሌ 9 ቀን ተሰጥቶአል

የፌደራል የመጀመርያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በነበቀለ ገርባ መዝገብና በሌሎች በአቃቤ ሕግና በፖሊስ በተያዙ  ተጠርጣሪዎች  ላይ ፖሊስ የጠየቀዉን የምርመራ ጊዜ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። ዛሬ በ 17 ተጠርጣሪዎች ላይ ፖሊስ ባቀረበዉ የክስ መዝገብ በተጠርጣሪዎች ላይ ከተያዙት ክሶች መካከል ብሔር ብሔረሰቦችን እንዲጋጩ በማድረግ ፤ የኦሮምያ ባለስልጣናትን የመግደል ሙከራ ፤ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን አስክሬን እንዲጉላላ በማድረግ የተሰኙት ክሶች ከብዙ ጥቂቶች መሆናቸዉ ተመልክቶአል። ከአቶ በቀለ ገርባ ጋር ዛሬ ፍርድቤት ከቀረቡት ውሰጥ ከ10 የአቶ ጀዋር መሐመድ አጃቢዎች ዘጠኙና የአቶ በቀለ ገርባ ሁለት ልጆች ይገኙበታል ። የወንጀሉ አፈፃፀም ዉስብስብነት በመግለፅ ፖሊስ ተጨማሪ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠዉ ቢጠይቅም ፖሊስ የጠየቀዉ የ 14 ቀናት ጊዜ ሊፈቀድለት አይገባም በሚል ጠበቆች በመከራከራቸዉ ፍርድ ቤቱ ዉሳኔ ለመስጠት ለሐምሌ 9 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱ ታዉቋል።

ዮሃንስ ገብረግዚአብሔር

ታምራት ዲንሳ 

ነጋሽ መሐመድ