1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት እንዴት እየሄደ ነው?

ሰኞ፣ ኅዳር 28 2013

በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት የተጎዱ ዜጎች ሰብዓዊ እርዳታ እንዲያገኙ ማድረግ፣ ግጭት ሸሽተው የተሰደዱትን መመለስ እና መሰረታዊ ግልጋሎቶችን መልሶ ማስጀመር የቀጣይ ዋናው የመንግሥት ትኩረት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አስታውቃል።የተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ እርዳታ ለማድረግ ውጊያ መቀጠሉ እንቅፋት እንደሆነበት ጠቅሷል።

https://p.dw.com/p/3mKSL
Äthiopien Konflikt in Tigray | Flüchtlinge in Sudan
ምስል Ashraf Shazly/AFP/Getty Images

በትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት እንዴታ

በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት የተጎዱ ዜጎች ሰብዓዊ እርዳታ እንዲያገኙ ማድረግ፣ ግጭት ሸሽተው ወደ ጎረቤት ሀገራት የተሰደዱትን መመለስ እና መሰረታዊ ግልጋሎቶችን መልሶ ማስጀመር የቀጣይ ዋናው የመንግሥት ትኩረት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት አስታውቃል።የተባበሩት መንግሥታት በበኩሉ በክልሉ ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረግ ውጊያ አሁንም መቀጠሉ እንቅፋት እንደሆነበት ጠቅሷል።በሌላ በኩል በትግራይ ክልል የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች የምግብ አቅርቦት መመናመን እንዳሳሰበውም ድርጅቱ አስታውቃል። በፌደራል መንግሥትና በትግራይ ክልላዊ መንግሥት መካከል የተፈጠረው ጦርነት መቀሌ በመከላከያ ሠራዊት እጅ መግባቷን ተከትሎ መጠናቀቁ ቢነገርም አሁንም ውጊያ አለማብቃቱ የሰብዓዊ ድጋፍ ሥራዎችን ለማከናወን አዳጋች መሆኑ ይነገራል።

ሰሎሞን ሙጬ

ታምራት ዲንሳ

አዜብ ታደሰ