ትምህርትአፍሪቃ
«ሌላ ዮንቨርስቲ ወስደው ያስተምሩን»
ሰኞ፣ ጥቅምት 1 2014ማስታወቂያ
ተማሪዎቹ እና የተማሪ ተወካዮች ለዶይቸ ቬለ እንዳሉት ከትግራይ ክልል ሲወጡ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርታቸውን እንደሚያስጨርሳቸው ቃል የገባ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ምንም ተጨባጭ ምላሽ አላገኙም። በክልሉ ካሉ ከአራቱም ዩኒቨርሲቲዎች ከ10 000 በላይ ተማሪዎች መኖራቸውን የተናገሩት አንድ ጥያቄ አቅራቢ በተለይ ለመመረቅ ወራቶች ቀርቷቸው የነበሩት ተማሪዎች ጉዳይ አሳሳቢ መሆኑን ገልፀዋል። ስለሆነም መንግሥት የእነዚህን ተማሪዎች ጭንቀት ተገንዝቦ ወደተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች መድቦ እንዲያስተምራቸው በሥፍራው ተገኝተው የነበሩ ወላጆችም ጠይቀዋል።
ሰለሞን ሙጬ
ልደት አበበ
ኂሩት መለሰ