1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ኤሌክትሪክ ስርጭት ጀመረ

ረቡዕ፣ ኅዳር 28 2015

የትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለን ጨምሮ መኮኒ፣ ውቅሮ፣ ዓዲግራት፣ ዓብይዓዲ እና ሌሎች በአካባቢው ያሉ ከተሞች ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኃይል ቋት የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት ጀመረ። ትግራይ ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኃይል ቋት ታገኘው የነበረ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሰኔ ወር 2013 ዓመተ ምህረት ወዲህ ተቋርጦ ነበር።

https://p.dw.com/p/4KcSB
Äthiopien | Straßenszene Mekele City
ምስል Million Gebresilassie/DW

መቀሌን ጨምሮ የተለያዩ የትግራይ ከተሞች ኤልኬትሪክ ማግኘት ጀመሩ

መቐለን ጨምሮ የተለያዩ የትግራይ ከተሞች ከ18 ወራት በኃላ ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የሐይል ቋት የኤሌክትሪክ ሐይል አቅርቦት ማግኘት ጀመሩ። መቐለ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሐይል ሰሜን ሪጅን ሠራተኞች ለዶቼቬለ እንዳረጋገጡት፣ከትናንት ማምሻ ጀምሮ የትግራይ ዋና ከተማ መቐለን ጨምሮ መኮኒ፣ ውቅሮ፣ ዓዲግራት፣ ዓብይዓዲ እና ሌሎች በአካባቢው ያሉ ከተሞች ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኃይል ቋት የኤሌክትሪክ ሐይል ማግኘት ጀምረዋል። ትግራይ ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የሐይል ቋት ታገኘው የነበረ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሰኔ ወር 2013 ዓመተ ምህረት ወዲህ ተቋርጦ ነበር። በዚህ መካከል በትግራይ ከሚገኝ የሐይል ምንጭ፣ በክልሉ አስተዳደር አስተባባሪነት የተቆራረጠ የኤሌክትሪክ ሐይል ለህዝቡ ይቀርብ ነበር።ትላንት ማክሰኞ ከ11 ሰዓት ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሐይል ቋት ለመቐለና ለተለያዩ የትግራይ ከተሞች መቅረብ መጀመሩ የሐይል እጦትን ያቃልላል ተብሎ እንደሚገመት አዜብ ታደሰ በስልክ ያነጋገረችው የመቀሌው ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ ገልጾልናል።

ሚሊዮን ኃይለ ሥላሴ
አዜብ ታደሰ