በትግራይ ክልል ውሳኔ ላይ የተሰጡ አስተያየቶች
ዓርብ፣ ጥቅምት 7 2012ማስታወቂያ
የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምሕርት ቢሮ የአንደኛ ዓመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የግጭት ስጋት አለብኝ ወደሚለው ወደ አማራ ክልል አልክም ማለቱ እያነጋገረ ነው። ውሳኔውን የደገፉ እርምጃው ተገቢ ነው ሲሉ የተቃወሙት ደግሞ የተማሪዎችን መብት የሚጋፋ እና ለፀብም የሚያነሳሳ ሲሉ ተችተውታል። የአማራ ክልልም የአጸፋ እርምጃ ከመውሰድ እንዲቆጠብ ያሳሰቡም አሉ። ዶቼቬለ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ፣ የፌደራል ትምህርት ሚኒስትርና የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስተር የሥራ ኃላፊዎች በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ቢጠይቅም «እየተወያየንበት ነው» ሲሉ መልሰዋል። የባሕርዳሩ ወኪላችን ዝርዝሩን ልኮልናል።
ዓለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ