በትግራዩ ዉግያ የቀይ መስቀል ሰብዓዊ ድጋፍ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 22 2013ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በትግራይ ክልል ልዩ ኃይል እና በመከላከያ ሠራዊት መካከል ጦርነት ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ሁሉንም የሰብዓዊ ግልጋሎቶች መስጠቱንና ወደፊትም የተጎዱትን ማቋቋም ላይ እንደሚሰራ ገለፀ። ከዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ጋር በመሆን ከአንድ ሺህ በላይ የተጠፋፉ ቤተሰቦችን ደኅንነት የማሳወቅ ተግባር መከወኑንም አስታውቃል። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ደግሞ ሰብዓዊ እርዳታዎች ተደራሽ እንዲሆኑ በትግራይ ክልል የተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች እንዲመለሱ ጠይቋል።
ሰለሞን ሙጬ
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሐመድ