1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሰሞኑ የህወሓት መግለጫዎች ላይ የምሁራን ትችት 

ማክሰኞ፣ መስከረም 26 2013

አስተያየት ሰጭዎቹ እንዳሉት  በኮሮና ምክንያት የተራዘመው ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ አሁን ኢትዮጵያን የሚያስተዳድረው መንግሥት ሕጋዊ ነው።ሥልጣኑም የተራዘመለት በሕጋዊ መንገድ መሆኑን አስረድተዋል። የአንድ ምሁር ደግሞ የትግራይን ክልልና የፌደራል መንግሥቱን የሚያገናኛቸው ብቸኛው የበጀት ጉዳይ  ሊያወዛግብ እንደሚችል ግምታቸውን ሰንዝረዋል።

https://p.dw.com/p/3jWvz
Emblem der Tigray People's Libration Font (TPLF)

በሰሞኑ የህወሓት መግለጫዎች ላይ የምሁራን ትችት 

የትግራይ ክልል ገዥ ፓርቲ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ፣ህወሓት፣የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት የሚያወጣቸው ሕጎች፣ ትዕዛዞችና ውሳኔዎች ከትናንት አንስቶ ተቀባይነት አይኖራቸውም ማለቱን  ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የአማራ ክልል ባለሥልጣን እና ምሁራን ተቹ። አስተያየት ሰጭዎቹ እንዳሉት  በኮሮና ምክንያት የተራዘመው ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ አሁን ኢትዮጵያን የሚያስተዳድረው መንግሥት ሕጋዊ ነው።ሥልጣኑም የተራዘመለት በሕጋዊ መንገድ መሆኑን አስረድተዋል።የትግራይ ክልልና የፌደራል መንግሥት ግንኙነት ተቋርጦ መቆየቱን ያስታወሱት አንድ ምሁር ደግሞ ሁለቱን የሚያገናኛቸው የበጀት ጉዳይ  ሊያወዛግብ እንደሚችል ግምታቸውን ሰንዝረዋል።ያነጋገራቸው አለምነው መኮንን ከባህርዳር ዝርዝሩን ልኮልናል።
አለምነው መኮንን
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ