1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስድስተኛው አገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫን ስለመታዘብ

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 2 2013

ስድስተኛው አገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትኃዊና ገለልተኛ እንዲሆን የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምርጫውን ለመታዘብ እንዲዘጋጁ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

https://p.dw.com/p/3mb7y
Logo | National Election Board of Ethiopia
ምስል National Election Board of Ethiopia

አሁንም ውጥረት የበዛበትና የሠላም እጦት የሚታይበት

ስድስተኛው አገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትኃዊና ገለልተኛ እንዲሆን የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምርጫውን ለመታዘብ እንዲዘጋጁ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥሪ ቀርቦላቸዋል። ከዚህ በፊት ምርጫዎችን እንደታዘቡ የተናገሩ ያነጋገርናቸው የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ነበረ ባሉት ምቹ ያልሆነ የፖለቲካ ምኅዳር፣ አፋኝ ሕጎችና የአቅም ማነስ ድርጅቶቹ ይህንን ትልቅ ኃላፊነት የመወጣት ሚና ነበራቸው ማለት እንደማያስደፍር ገልፀዋል። አሁንም ውጥረት የበዛበትና የሠላም እጦት የሚታይበት የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ምርጫን ለመታዘብ ምቹ ባይሆንም ፣ መራጮችን በማስተማር ፣ በማንቃትና ጫና እንዳይደርስባቸው በማድረግ ሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶቹ እንደሚንቀሳቀሱ ተናግረዋል።


ሰለሞን ሙጬ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ