1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስደተኞች እና የአውሮጳ የፍልሰት ፖሊሲ

ሐሙስ፣ መስከረም 17 2011

ሰሞኑን ከሊቢያ የባህር ጠረፍ የታደገቻቸውን 58 ስደተኞች ያሳፈረችው አኳሪየስ የተባለችው የነፍስ አድን መርከብ ማረፊያ ፍለጋ ቆይታ ወደ ፈረንሳይ ማርሴይ ወደብ ብታቀናም ለጊዜው ተቀባይነት ሳታገን መቅረቷ ይታወሳል።

https://p.dw.com/p/35aSn
Rettungsschiff Aquarius
ምስል picture-alliance/dpa/R. Runza

ይሁንና፣ ፈረንሳይ  ቆየት ብላ አቋሟን በማለሳለስ በመረከቧ አኳሪየስ ከተሳፈሩት ስደተኞች መካከል 18 ን ተቀብላለች። ቀሪዎቹን ስደተኞች ደግሞ ጀርመን፣ ስጳኝ፣ ማልታ እና ፖርቱጋል ተከፋፍለው ለመቀበል ተስማምተዋል። ይሁንና፣ የፓናማ መንግሥት የዚችኑ በሜድትሬንየን ባህር  ስደተኞችን ከሚያጋጥማቸው የመስመጥ አደጋ በማዳኑ ተግባር ላይ የተሰማራችውን አኳርየስ የተባለችውን መርከብ ፈቃድ ሰሞኑን ያነሳበት ድርጊት ኅልውናዋን አደጋ ላይ ጥሎታል። ይህን ተከትሎ ጉዳዩ ያሳሰባቸው  ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና መሰል ተቋማት የአውሮጳ ህብረት ሀገራት ተደጋግሞ ለሚታየው ቀውስ አፋጣኝ መፍትሔ እንዲፈልጉለት ጠይቀዋል።  

ሀይማኖት ጥሩነህ

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ