የቤንች ሸኮ ዞን ነዋሪዎች አቤቱታ
ረቡዕ፣ ኅዳር 8 2014ማስታወቂያ
የቤንች ሸኮ ዞን ፖለቲከኞችና የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት ከደቡብ ክልል በመነጠል የራሱን ክልል ለማደራጀት በዝግጅት ላይ ለሚገኘው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የተካሄደው የማዕከል ከተሞች ምርጫ በጋራ የተደረሱ ስምምነቶችን የጣሰ ነው በማለት ቅሬታቸውን ለፌደራሉ መንግስት አቀረቡ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች የሕዝበ ውሳኔ ማስጸፈሚያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት በበኩለ የማዕከል ከተሞች ምርጫ የተከናወነው በግልፅ በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት ነው ሲል ዐስታውቋል።
ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ኂሩት መለሰ