1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ስለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የነዋሪዎችና የሕግ ባለሙያ አስተያየት

ሐሙስ፣ ጥቅምት 25 2014

ጦርነቱ በተለይም ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ወደ አጎራባች አከባቢዎች መስፋፋቱን ተከትሎ በተለያዩ አከባቢም የአለመረጋጋትን ስጋት በማጫሩ የአዋጁን አስፈላጊነት የሚጋሩ ዜጎችም በርካቶች ናቸው።

https://p.dw.com/p/42ago
Äthiopien Stadtbild Adis Abeba mit Schriftzug
ምስል Seyoum Getu/DW

«አስፈላጊነቱን የሚያምኑ ጥቂት አይደሉም»

መፍትሄ አልባ ሆኖ ተባብሶ የቀጠለውን አንድ ዓመት የደፈነ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን ተክትሎ ኢትዮጵያ ያወጀችው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዛሬ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ወደ ተግባር ገብቷል። ጦርነቱ በተለይም ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ወደ አጎራባች አከባቢዎች መስፋፋቱን ተከትሎ በተለያዩ አከባቢም የአለመረጋጋትን ስጋት በማጫሩ የአዋጁን አስፈላጊነት የሚጋሩ ዜጎችም በርካቶች ናቸው። አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡት የሕግ ተንታኝ እንዳሉትም በመደበኛ ጊዜ የሚጠበቁትን ሰብዓዊ መብቶች ሊደፈጥጥ የሚችለውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጅ ባይወደድም ለአሁናዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ አስፈላጊ ነው ይላሉ።

ስዩም ጌቱ 

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ